ቌንቌ | Language
     
 
መግቢያ
     
 
Banner

የካቲት 20 ቀን 2003 ዓ.ም የማሟያ ምርጫ

3:30

የካቲት 20 ቀን 2003 ዓ.ም የማሟያ ምርጫ

3:45

የካቲት 20 ቀን 2003 ዓ.ም የማሟያ ምርጫ

3:50

የካቲት 20 ቀን 2003 ዓ.ም የማሟያ ምርጫ

4:00

የካቲት 20 ቀን 2003 ዓ.ም የማሟያ ምርጫ

 

የመራጮች እና የስነዜጋ ትምህርት በየክልሉ የሬዲዮ የመገናኛ ብዙኃን

ከጥቅምት 1 ቀን 2ዐዐ4 ዓ.ም. ጀምሮ መሠራጨቱን በተመለከተ

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጠ መግለጫ

 

በተሻሻለው የምርጫ ህግ አዋጅ ቁጥር 532/1999 ዓ.ም. አንቀጽ 89 እንደተደነገገው፤

-     ቦርዱ የተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎችን በመጠቀም መራጩ ስለምርጫው በቂ ግንዛቤ የሚያገኝበት ስልት በመቀየስ የመራጮች እና የስነዜጋ ትምህርት ይሰጣል፣

 

-     ቦርዱ የመራጮች እና የስነዜጋ ትምህርት በሌላ ድርጅት መስጠት አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው የማስተማር ፈቃድ ሊሰጥ ይችላል፣

 

-     ቦርዱ አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው አግባብ ካለው አካል ጋር በመዋዋል የመራጮችና የስነዜጋ ትምህርት እንዲሰጥ ሊያደርግ ይችላል፡፡

 

በዚሁ መሠረት ቦርዱ ቀደም ባሉ ምርጫዎች ሲሰጥ የነበረው የመራጮችና የስነዜጋ ትምህርት ወጥነት እና ተከታታይነት የሌለው እንደነበር በማረጋገጥ ይህንኑ ችግር ለመቅረፍ የሚያስችል የማስተማሪያ ሰነድ አዘጋጅቶ በ2ዐዐ2 ዓ.ም. ጠቅላላ ምርጫ ተግባራዊ አድርጓል፡፡

ሰነዱ በወቅቱ ቦርዱ ባዘጋጃቸው የተለያዩ አውደጥናቶች ላይ በመስኩ ባለሙያዎች በጥልቀትና በስፋት ተገምግሟል፡፡ በመሆኑም ጥሩ ግብአት አግኝቷል፡፡ በዚሁ መሠረት ቦርዱ በ2ዐዐ2 ዓ.ም. በተካሄደው ጠቅላላ ምርጫ የማስተማሪያ ሰነዱ በመገናኛ ብዙኃንና በተለያዩ የትምህርት መስጫ ዘዴዎች ለመራጩ ሕዝብ ተገቢውን የምርጫ አፈፃፀም መረጃ እንዲደረስ አድርጓል፡፡ ስለሆነም ሰነዱ ለምርጫው ስኬታማነት ከፍ ያለ አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡

ቦርዱ በ2ዐዐ2 ዓ.ም. የሰነዱ ትግበራ ላይ ያገኛቸውን ተሞክሮዎችን፣ በሀገር ውስጥ እና በውጪ አውደ ጥናቶች ላይ በተለያዩ ጊዜያት የቀሰማቸውን ልምዶችና ተሞክሮዎች፣  ከበርካታ ተቋማትና ባለሙያዎች በቂ ግብዓት ከአገኘ በኋላ ሰነዱን ወደ ማኑዋል/መጽሐፍ ለውጦታል፡፡

ማኑዋሉ በአማርኛ  እና በተለያዩ የክልል የሥራ ቋንቋዎች ማለትም በትግርኛ፣ በአፋርኛ፣ በኦሮምኛ፣ እና በሶማሊኛ ቋንቋዎች ተተርጉሞ በህትመት ላይ ይገኛል ፡፡ በተጨማሪም በደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ክልል በስፋት ከሚነገሩ እና በዩኒቨርስቲ አና በኰሌጅ ደረጃ ትምህርት በሚሰጥባቸው በሲዳምኛ፣ በሀድይኛ፣ በወላይትኛ፣ በጋሞኛ እና በከፊቾ ቋንቋዎች ትርጉሙ እየተጠናቀቀ ይገኛል፡፡ በመሆኑም በቅርብ ቀን ውስጥ ወደ ህትመት ይገባል ተብሎ የታመናል፡፡ በተጨማሪም በሐረሪ ቋንቋ ለማስተርጐም በሂደት ላይ እንገኛለን፡፡ በቀጣይም በተጨማሪ በሌሎች የሀገሪቱ ቋንቋዎች ደረጃ በደረጃ ተተርጉሞ ለመራጩ ሕዝብ የሚደርስበት ሁኔታ ይመቻቻል፡፡

በአሁኑ ጊዜ ይህን ማኑዋል በመጠቀም የመራጮችና የስነዜጋ ትምህርትን ለየክልሉ ሕዝብ በተገቢው ሁኔታ ለማድረስ በየክልሉ የመገናኛ ብዙኃን አማካይነት በሬዲዮ በስፋት እንዲሰራጭ የአየር ሰዓት ግዢ እና የሥርጭት ውል በቦርዱ ጽ/ቤት ተፈፅሟል፡፡ በተጨማሪም ከኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት እና ከፋና ብሮድካትስ ኮርፖሬት ጋር የመራጮችና የስነዜጋ ትምህርት በሬዲዮ ለአንድ ዓመት ለመስጠት የሚያስችል የውል ስምምነት ፈጽሟል፡፡

በዚህ ረገድ የትምህርቱ አሰጣጥ ዘዴ ወጥነት እንዲኖረው ከፌዴራልና ከክልል መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ጋር የጋራ ምክክርና ውይይት ተካሂዷል፡፡ ለዚህም የሥራ ቅልጥፍና የመራጮችና የስነዜጋ ትምህርቱን ተግባራዊ ለማድረግ የቦርዱ እና የጽሕፈት ቤቱ አመራር ከሁሉም ክልል መንግሥታት ርዕሰ መስተዳድሮች ጋር በመመካከር ስኬታማ እና ቀጣይነት ባለው መልኩ እንዲሰጥ ሁኔታዎችን አመቻችቷል፡፡

ስለሆነም መላው የሀገራችን ህዝቦች ከጥቅምት 1 ቀን 2ዐዐ4 ዓ.ም. ጀምሮ በቀጣይነት ከላይ በተጠቀሱት የክልል የመገናኛ ብዙኃን እና ሬዲዮ ጣቢያ የሚተላለፈውን የመራጮች እና የስነዜጋ ትምህርት በንቃት እንድትከታተሉት፣ ንቁ ተሳትፎ እንድታደርጉ እና ገንቢ አስተያየት እንድትሰጡበት ቦርዱ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ በተጨማሪም ይህንኑ ለማጠናከር በስርጭት ረገድ በስፋት ተደማጭ በሆኑት የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት እና የሬዲዮ ፋና ብሮድካስት ኮርፖሬት አማካይነት ትምህርቱ በሀገሪቱ ዋና ዋና ቋንቋዎች ይሰጣል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

መስከረም 3ዐ ቀን 2ዐዐ4 ዓ.ም.

አዲስ አበባ፡፡


2003 .. በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ በደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች

 

እና

በኦሮሚያ ክልሎች የተካሄደው የማሟያ ምርጫ ውጤት ማጠቃለያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ2003 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ በደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በኦሮሚያ ክልሎች የማሟያ ምርጫ እንዲካሔድላቸው በጠየቁት መሠረት፡-

1. በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር

  • የከተማው አስተዳደር - 12
  • የክፍለ ከተማ እና - 866
  • የወረዳ ምክር ቤቶች 10,126 አባላት የማሟያ ምርጫ

2. በደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል

  • በሲዳማ ዞን ወንዶ ገነት ወረዳ - 14 ቀበሌዎች

የዞን፣ የወረዳ እና የቀበሌ ምክር ቤት አባላት ማሟያ ምርጫ

  • በቤንች ማጂ ዞን ሸኮ ወረዳ - 24 ቀበሌዎች

የዞን፣ የወረዳ እና የቀበሌ ምክር ቤት አባላት ማሟያ ምርጫ

  • በአሌ ልዩ ወረዳ - 17 ቀበሌዎች

የወረዳ እና የቀበሌ ምክር ቤት አባላት ማሟያ ምርጫ

3. በኦሮሚያ ክልል

  • በምዕራብ አርሲ ዞን ወንዶ ወረዳ - 4 ቀበሌዎች

የወረዳ እና የቀበሌ ምክር ቤት አባላት ማሟያ ምርጫ

ለማካሔድ የምርጫ አፈፃፀም የጊዜ ሠሌዳ አውጥቶ ለሕዝብ ይፋ ማድረጉ የሚታወስ ነው፡፡

በዚሁ መሠረት የማሟያ ምርጫው የካቲት 20 ቀን 2003 ዓ.ም. በተሳካ መልኩ ተካሂዷል፡፡

የመራጩ ሕዝብ ተሳትፎ

.

ክልል /አስተዳደር

የተመዘገበ መራጭ ሕዝብ

ድምፅ የሰጠ ሕዝብ

ድምፅ ያልሠጠ

ሴት

ወንድ

ድምር

ሴት

ወንድ

ድምር

ሴት

ወንድ

ድምር

1

አዲስ አበባ

363,104

336,879

699,983

283,756

243,453

527,209

79,348

93,426

172,774

2

ኦሮሚያ

6,021

6,994

13,015

5,937

6,851

12,788

84

143

227

3

ደቡብ ብ/ብ/ሕ

31,245

36,092

67,337

28,595

33,347

61,942

2,650

2,745

5,395

 

በጠቅላላው በአዲስ አበባ ከተማ፣ በደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች እና በኦሮሚያ ክልሎች በማሟያ ምርጫ፣

የተመዘገበ መራጭ ሕዝብ

ድምፅ የሰጠ ሕዝብ

ድምፅ ያልሠጠ

ሴት

ወንድ

ድምር

ሴት

ወንድ

ድምር

ሴት

ወንድ

ድምር

400,370

379,965

780,335

318,288

283,651

601,939

82,082

96,314

178,396

 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት ባካሔደው 011ኛ/2003 መደበኛ ስብሰባው የካቲት 20 ቀን 2003 ዓ.ም. የተካሄደውን የማሟያ ምርጫ ውጤት መርምሮ አፅድቆታል፡፡ ውጤቱም ከዚህ እንደሚከተለው ይፋ ሆኗል፡፡

የማሟያ ምርጫው ውጤት

1. አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር

  • ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ለ12 የተጓደሉ መቀመጫዎች የተወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎች፡-
  • ኢህአዴግ

ወንድ

9

ሴት

3

ድምር

12

  • መኢብን

ወንድ

1

ሴት

-

ድምር

1

  • ኦነአግ

ወንድ

1

ሴት

-

ድምር

1 ናቸው፡፡

 

የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) 12 መቀመጫዎችን ሙሉ በሙሉ አግኝቷል፡፡

  • ለክፍለ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ለ866 የተጓደሉ መቀመጫዎች የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) ወንድ 661 ሴት 205 ድምር 866 ዕጩዎች አቅርቦ ሙሉ በሙሉ አግኝቷል፡፡
  • ለወረዳ አስተዳደር ምክር ቤት ለ10,126 የተጓደሉ መቀመጫዎች የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) ወንድ 6,301 ሴት 3,825 ድምር 10,126 ዕጩዎች አቅርቦ ሙሉ በሙሉ አግኝቷል፡፡

2. የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል

  • ለዞን አስተዳደር ምክር ቤት ለ 10 የተጓደሉ መቀመጫዎች የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢህዴን - ኢህአዴግ) ወንድ 8 ሴት 2 ድምር 10 ዕጩዎች አቅርቦ ሙሉ በሙሉ አግኝቷል፡፡
  • ለወረዳ አስተዳደር ምክር ቤት ለ 111 የተጓደሉ መቀመጫዎች የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢህዴን - ኢህአዴግ) ወንድ 91 ሴት 20 ድምር 111 ዕጩዎች አቅርቦ ሙሉ በሙሉ አግኝቷል፡፡
  • ለቀበሌ አስተዳደር ምክር ቤት ለ 9,030 የተጓደሉ መቀመጫዎች የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢህዴን - ኢህአዴግ) ወንድ 8,029 ሴት 1,001 ድምር 9,030 ዕጩዎች አቅርቦ ሙሉ በሙሉ አግኝቷል፡፡

3. ኦሮሚያ ክልል

  • ለወረዳ አስተዳደር ምክር ቤት ለ 12 የተጓደሉ መቀመጫዎች የኦሮሞ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦህዴድ - ኢህአዴግ) ወንድ 9 ሴት 3 ድምር 12 ዕጩዎች አቅርቦ ሙሉ በሙሉ አግኝቷል፡፡
  • ለቀበሌ አስተዳደር ምክር ቤት ለ 1,200 የተጓደሉ መቀመጫዎች የኦሮሞ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦህዴድ - ኢህአዴግ) ወንድ 1,115 ሴት 85 ድምር 1,200 ዕጩዎች አቅርቦ ሙሉ በሙሉ አግኝቷል፡፡

 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

መጋቢት 2 ቀን 2003 ዓ.ም.

አዲስ አበባ፡፡

 

 


ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጽ/ቤት

ለመንግስታዊና መንግስታዊ ላልሆኑ ድርጅቶችና ፋብሪካዎች

የተላለፈ ጥሪ

የካቲት 20 ቀን 2003 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው የማሟያ ምርጫ አፈጻጸም የጊዜ ሠሌዳ መሠረት በአዲስ አበባ ከተማ በሁሉም ወረዳዎች፣ በደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ክልል በወንዶ ገነት፣ በአሌ እና ሸኮ ወረዳዎች፣ በኦሮሚያ ክልል በወንዶ ወረዳ በዛሬው ዕለት የድምፅ አሠጣጡ ሂደት ከማለዳው 12፡00 ሰዓት ጀምሮ በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

በማሟያ ምርጫው ለመሳተፍ ተመዝግበው የመራጮች ምዝገባ መታወቂያ ካርድ የያዙ መራጮች በዛሬው ዕለት በስራ ላይ የሚገኙ እንዳሉ ተረጋግጧል፡፡

በመሆኑም በተለይም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውስጥ የምትገኙ መንግሥታዊ፣ የግል ድርጅቶች እንዲሁም ፋብሪካዎች የመራጮች ምዝገባ ካርድ ይዘው የሚገኙ ሠራተኞች በምርጫ የመሳተፍ ህገ መንግሥታዊ መብታቸውን ተግባራዊ ለማድረግ እንዲችሉ ፈቃድ በመስጠት እንድትተባበሩ ቦርዱ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጽ/ቤት

አዲስ አበባ፡፡

 


 

 

ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የማሟያ ምርጫ የድምፅ መስጫ ዕለቱን አስመልክቶ

የተላለፈ ጥሪ

 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የካቲት 20 ቀን 2003 ዓ.ም የማሟያ ምርጫ ለማካሄድ አስፈላጊውን ዝግጅት በተሳካ ሁኔታ አጠናቋል፡፡

የማሟያ ምርጫ በሚካሄድባቸው በአዲስ አበባ ከተማ በሁሉም ወረዳዎች፣ በኦሮሚያ ክልል በወንዶ ወረዳ፣ በደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል በወንዶገነት፣ አሌና ሸኮ ወረዳዎች በነገው ዕለት መራጮች ድምጽ ይሰጣሉ፡፡

ቦርዱ ምርጫውን ለማካሄድ የሚያስፈልጉ የድምጽ መስጫ ሰነዶችና ቁሳቁሶች በበቂ መጠን ተዘጋጅተው ለሁሉም አካባቢዎች በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች በወቅቱ እንዲደርስ አድርጓል፡፡

የመራጮችና እጩዎች ምዝገባ በተሳካ ሁኔታ በሁሉም አካባቢዎች ተጠናቆ መራጩ ህዝብም በአካባቢው በየደረጃው ከሚገኙ ምክርቤቶች የተጓደሉ የምክርቤት አባላትን ለማሟላት የድምጽ መስጫ ቀኑን እየተጠባበቀ ይገኛል፡፡ የምርጫ አስፈጻሚዎችም የህዝብ ታዛቢዎችን አሟልተው፣ የተወዳዳሪ ወኪሎችን በወቅቱ እንዲመደቡ በማድረግ እና የምርጫ ጣቢያዎችን በተገቢው ሁኔታ አደራጅተው ዕለቱን በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ፡፡

ስለሆነም መራጩ ህዝብ ህገ መንግስታዊ መብቱን በመጠቀም በነፃነት የሚፈልገውን ተወዳዳሪ መምረጥ እንዲችልና የድምጽ አሰጣጥ ሂደቱ ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የሁሉንም ወገኖች መልካም ትብብርና ድጋፍ ይፈልጋል፡፡

በመሆኑም መራጮች በነገው ዕለት ከማለዳው 12:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ 12፡00 ሰዓት ድረስ የምርጫ ካርዳችሁን ይዛችሁ በየተመዘገባችሁበት የምርጫ ጣቢያ በግንባር በመገኘት በነፃነት ድምፃችሁን እንድትሰጡ ቦርዱ በአክብሮት ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የካቲት 19 ቀን 2003 ..

አዲስ አበባ



2003 .. ለሚካሄደው ማሟያ ምርጫ የተመዘገቡ መራጮች ብዛት


 

ተራ

ቁጥር

 

ክልል

የመራጭ ህዝብ ብዛት

ወንድ

ሴት

ድምር

1

አዲስ አበባ

 

331,291

360,876

692,167

2

ኦሮሚያ

 

6,941

6,044

12,985

3

ደቡብ ብሔሮች፣ብሔረሰቦችና ህዝቦች

 

35,970

31,127

67,217

ጠቅላላ ድምር

 

374,832

398,047

772,369



 

ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የመራጮች የምዝገባ ጊዜ መራዘምን አስመልክቶ

የተሰጠ መግለጫ

 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥር 26 ቀን ባካሄደው 004ኛ አስቸኳይ ስብሰባው የመራጮች ምዝገባ ጊዜ እንዲራዘም ከተወዳዳሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የቀረበን ጥያቄ እና ቦርዱ ቀደም ሲል የመራጮች ምዝገባ በተመለከተ አቅዶት የነበረውን ጊዜ መርምሯል፡፡

 

በማሟያ ምርጫው አፈፃፀም የጊዜ ሠሌዳ መሠረት የመራጮች ምዝገባ እየተከናወነ ቢሆንም እስከ አሁን በተካሄደው የምዝገባ ቀናት በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ የሚጠበቀውን ያህል መራጮች መመዝገብ አለመቻላቸውን ቦርዱ አረጋግጧል፡፡ ከተወዳዳሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የቀረበው የማራዘም ጥያቄ አግባብነት ያለውና ቦርዱ መራጮች በንቃትና በስፋት እንዲሳተፉ ካለው ፍላጐት በመነሳት የመራጮች ምዝገባ ለ7 ተከታታይ ቀናት እንዲራዘም ወስኗል፡፡

 

በመሆኑም ጥር 29 ቀን 2ዐዐ3 ዓ.ም. ይጠናቀቅ የነበረው የመራጮች ምዝገባ ጊዜ እስከ የካቲት 6 ቀን 2ዐዐ3 .ም. ድረስ መራዘሙን ቦርዱ የማሟያ ምርጫ ለሚካሄድባቸው አካባቢ ሕዝቦች ያሳስባል፡፡ የማሟያ ምርጫ በሚካሄድባቸው አካባቢዎች የምትገኙ የአስተዳደር አካላትና ተወዳዳሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተራዘመው የመራጮች ምዝገባ ጊዜ በመጠቀም ሕዝቡ የምርጫ ካርዱን እንዲይዝ ተገቢውን ቅስቀሳ እንድታደርጉ ቦርዱ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

 

በየደረጃው የምትገኙ የምርጫ አስፈፃሚዎችም በተራዘመው የመራጮች የምዝገባ ጊዜ ሠሌዳ መሠረት መራጮችን እየተቀበላችሁ በህጉ መሠረት እንድትመዘግቡ ቦርዱ በጥብቅ ያሳስባል፡፡

 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ጥር 28 ቀን 2ዐዐ3 ዓ.ም.

አዲስ አበባ

 


ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

በኦሮሚያ፣ በደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል እና በአዲስ አበባ

ከተማ አስተዳደር በየደረጃው የሚገኙ ምከር ቤቶች አባላት የማሟያ ምርጫ

አፈፃፀመ የጊዜ ሠሌዳ አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ

 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ታህሳስ 28 ቀን 2ዐዐ3 .. ባካሔደው አስቸኳይ ስብሰባው ከኦሮሚያ፣ ከደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ክልሎች እና ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በየደረጃው ከሚገኙ ምክርቤቶች በተለያዩ ምክንያቶች በተጓደሉ የምክር ቤት አባላት እና ምርጫ ባልተካሄደባቸው ቀበሌዎች ላይ የማሟያ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስፈልገውን የጊዜ ሠሌዳ መርምሮ አጽድቋል፡፡

 

ቦርዱ በተሻሻለው የምርጫ ህግ እዋጅ ቁጥር 532/1999 .. አንቀጽ 3ዐ መሠረት፡-

 

1ኛ. ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር

  • 12 የከተማ አስተዳደር ምክር ቤት አባላት፣
  • 870 የክፍለ ከተማ ምክር ቤት አባላት፣
  • 10,185 የወረዳ ምክር ቤት አባላት

በድምሩ 11,067 የምክር ቤት አባላት ማሟያ ምርጫ፣

 

2ኛ. በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ አርሲ ዞን ሻሸመኔ ወረዳ በህዝበ ውሣኔ ወደ ክልሉ ለመተዳደር የመረጡ 4 ቀበሌዎች ላይ

  • የቀበሌና የወረዳ ምክር ቤት አባላት ማሟያ ምርጫ፣

 

3. በደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል

 

  • በሲዳማ ዞን በወንዶ ገነት ወረዳ በሕዝበ ውሳኔ ወደ ክልሉ ለመተዳደር የመረጡ 14 ቀበሌዎች፣

  • በጋሞጐፋ ዞን አዲስ በተመሠረተው አሌ ወረዳ 17 ቀበሌዎች፣

  • በቤንች ማጂ ዞን ሸኮ ወረዳ 24 ቀበሌዎች

ላይ የቀበሌ የወረዳና የዞን ምክር ቤቶች አባላት ማሟያ ምርጫ

በህጉ መሠረት በ3 ወር ጊዜ ውስጥ ለማካሔድ የሚያሰፈልገውን የማሟያ ምርጫ አፈፃፀም የጊዜ ሠሌዳ ቀደም ሲል ከ38 የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ተገቢውን ምክክር በማድረግና አስተያየታቸውን በማካተት ከዚህ እንደሚከተለው አጽድቆ ይፋ አድርጓል፡፡

 

 

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

በኦሮሚያ፣ በደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል እና በአዲስ አበባ

ከተማ አስተዳደር በየደረጃው የሚገኙ ምክር ቤቶች አባላት የማሟያ ምርጫ

አፈፃፀም የጊዜ ሠሌዳ

 

ተቁ

ክንውን

ቀን

1

በምርጫው የሚወዳደሩ የፖለቲካ ድርጅቶች በቦርዱ ዋና ጽሕፈት ቤት ተገኝተው የመወዳደሪያ ምልክታቸውን የሚመርጡበት፡፡

 

ጥር 1ዐ ቀን 2ዐዐ3 ..

2

በየደረጃው የሚገኙ የምርጫ ጽሕፈት ቤቶች ተከፍተው ሥራቸውን የሚጀምሩበት፡፡

 

ጥር 13 ቀን 2ዐዐ3 ..

3

የግል ዕጩዎች ያሰባሰቡትን የድጋፍ ፊርማ ለማጣራት የቀበሌ አስተዳደር ጽሕፈት ቤቶች ክፍት ሆነው የሚቆዩበት፡፡

 

ጥር 14 ቀን እስከ ጥር 24 ቀን 2ዐዐ3 ..

4

በግል ለመወዳደር የሚፈልግ የድጋፍ ፊርማ የሚያሰባስብበትና ያሰባሰበውን የድጋፍ ፊርማ ለቀበሌ አስተዳደር ጽሕፈት ቤት በማቅረብ የሚጣራበት፡፡

 

ጥር 14 ቀን እስከ ጥር 24 ቀን 2ዐዐ3 ..

5

የሕዝብ ታዛቢዎች በየቀበሌው በሕዝብ የሚመረጡበት፡፡

 

ጥር 15 ቀን 2ዐዐ3 ..

6

የምርጫ ጣቢያዎች ተከፍተው ሥራቸውን የሚጀምሩበት

 

ጥር 16 ቀን 2ዐዐ3 ..

7

የመራጮች ምዝገባ በየምርጫ ጣቢያ የሚካሄድበት፡፡

 

ከጥር 20 ቀን እስከ ጥር 29 ቀን 2ዐዐ3 ..

8

የመራጮች መዝገብ በየምርጫ ጣቢያው ለሕዝብ ግልፅ ሆኖ የሚቆይበት

 

ከጥር 3ዐ እስከ የካቲት 4 ቀን 2ዐዐ3 ..

9

ተወዳዳሪ የፖለቲካ ድርጅቶች በሕጉ መሠረት በየሚወዳደሩበት የምርጫ ጽሕፈት ቤት የዕጩዎቻቸውን ዝርዝር በማቅረብ የሚያስመዘግቡበት፡፡

 

ከጥር 2ዐ እስከ ጥር 29 ቀን 2003 ..

10

በግል ለመወዳደር የድጋፍ ፊርማ የሚያሰባስቡበት እንዲጣራ የሚያደርጉበት እና ለምርጫ ክልል ጽሕፈት ቤት በማቅረብ በዕጩነት የሚመዘገቡበት፡፡

 

ከጥር 2ዐ እስከ ጥር 29 ቀን 2003 ..

11

የተጠቋሚ ዕጩዎች የአቤቱታ ይግባኝ ውጤት መጠባበቂያ፡፡

 

ጥር 3ዐ እና የካቲት 1 ቀን 2ዐዐ3 ዓም.

12

የዕጩዎች ስም ዝርዝር ለሕዝብ ይፋ የሚደረግበትና የዕጩነት መታወቂያ የሚሰጥበት፡፡

 

የካቲት 2 እስከ የካቲት 17 ቀን 2ዐዐ3 ..

13

የዕጩዎች የምርጫ ውድድር እንቅስቃሴ በይፋ የሚጀመርበት እና የሚጠናቀቅበት፡፡

 

ከየካቲት 2 እስከ የካቲት 17 ቀን 2ዐዐ3 ..

14

ለመራጮች የአንድ ቀን ገለፃ የሚሰጥበት፡፡

 

የካቲት 13 ቀን 2ዐዐ3 ..

15

የድምፅ መስጫ ቀን፡፡

 

የካቲት 2ዐ ቀን 203 .. እስከ ምሽቱ 12፡ዐዐ ሰዓት

 

16

የድምፅ ቆጠራ በየምርጫ ጣቢያው የሚከናወንበት፡፡

 

የካቲት 2ዐ ቀን 203 .. ከምሽቱ 12፡ዐዐ ሰዓት ጀምሮ

 

17

የድምፅ ቆጠራ ውጤት በየምርጫ ጣቢያው ለሕዝብ በይፋ የሚገለፅበት፡፡

 

የካቲት 21 ቀን 2ዐዐ3 ..

 

18

የማሟያ ምርጫ አጠቃላይ ውጤት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሚፀድቅበት እና ውጤቱ ለሕዝብ ይፋ የሚደረግበት፡፡

 

መጋቢት 2 ቀን 2ዐዐ3 ..

 

 

ማሳሰቢያ፣ በማሟያ ምርጫ የምትወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከዚህ በላይ በተዘረዘረው የጊዜ ሠሌዳ መሠረት ዕጩዎቻችሁን እንድታስመዘግቡ ቦርዱ በድጋሚ ያስታውቃል፡፡

 

በየደረጃው የምትገኙ የምርጫ አሰፈፃሚዎችም ይህንኑ አውቃችሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ከወዲሁ እንድታደርጉ ቦርዱ ያሳስባል፡፡

 

ታህሳስ 30 ቀን 2003 ..

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

አዲስ አበባ፡፡

 


 

 

 

ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የተሰጠ መግለጫ

 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በህገ መንግሥቱ፣ በተሻሻለው የምርጫ ህግ እና በተሻሻለው የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ ህግ በተሰጠው ሥልጣንና ኃላፊነት መሠረት የፖለቲካ ፓርቲዎችን በመመዝገብና እንቅስቃሴያቸውን በመከታተል፤ በመላ ሀገሪቱ በተለያዩ ጊዜያት የተካሄዱ የተለያዩ ምርጫዎችን በገለልተኝነትና ሙያዊ ብቃቱን ባስመሰከረ መልኩ ያስፈፀመ እና ለወደፊትም በተሻለ መልኩ ይህንኑ ተግባሩን አጠናክሮ ለማስቀጠል መጠነ ሰፊ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ የሚገኝ የዴሞክራሲ ተቋም ነው፡፡

 

ቦርዱ በተሻሻለው የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 573/2ዐዐዐ ዓ.ም. አንቀፅ 9 መሠረት የፖለቲካ ፓርቲዎችን የመመዝገብ፣ እንቅስቃሴያቸውን የመከታተልና የመቆጣጠር እና በአዋጁ አንቀፅ 39 መሠረት ህጉን አሟልተው ባልተገኙ ጊዜ የመሠረዝ ሥልጣን እና ኃላፊነት እንዳለው ተደንግጓል፡፡

 

የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንቅስቃሴ በመከታተልና በመቆጣጠር ሂደት ፓርቲዎች በህጉ የተቀመጡትን ድንጋጌዎች አሟልተው እንዲንቀሳቀሱ የተለያዩ የአቅም ግንባታ ሥራዎችን ሲሰራ የነበረ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ህጉን ሳያሟሉ በተገኙና ማስተካከያ እንዲያደርጉ እገዛ ተደርጎላቸው ያላሟሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ላይ ሕጋዊ እርምጃ መውሰድ እንዳለበት ቦርዱ ያምናል፡፡

 

በአሁኑ ጊዜ በቦርዱ ዕውቅና ያላቸው እና ህጉ የሚጠይቀውን አሟልተው በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኙ 22 ሀገር አቀፍና 54 ክልላዊ በጠቅላላው 76 የፖለቲካ ፓርቲዎች ናቸው፡፡ ቀሪዎቹ ውህደት የፈጠሩ ሲሆኑ ሌሎቹ የፖለቲካ ፓርቲዎች ደግሞ ከተመዘገቡ ረጅም ዓመታት ቢያስቆጥሩም እስከአሁን ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ የሌላቸው በስም ብቻ የሚታወቁ፣ በሕጉ መሠረት በሁለት ተከታታይ የምርጫ ዘመን ማለትም የጠቅላላ ወይም የአካባቢ ምርጫ ያልተሳተፉ፣ አድራሻ የሌላቸውና በመገናኛ ብዙኃን በተደጋጋሚ ቀርበው ሪፖርት እንዲያደርጉ ጥሪ ተደርጎላቸው መልስ ያልሰጡና ያልተገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ቦርዱ ኅዳር 3 ቀን 2ዐዐ3 ዓ.ም. ባካሄደው ዐዐ5/ዐ3 መደበኛ ስብሰባው በህጉ መሠረት ሠርዟቸዋል፡፡

 

ስለሆነም በአሁኑ ጊዜ በቦርዱ ዕውቅና ያላቸው እና በህጉ መሠረት የተቀመጡትን ድንጋጌዎች አሟልተው በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኙ 22 ሀገር አቀፍና 54 ክልላዊ በጠቅላላው 76 የፖለቲካ ፓርቲዎች ከዚህ የሚከተሉት ናቸው፡፡

ተራ ቁጥር

የፖለቲካ ፓርቲው መጠሪያ

አህፅሮተቃል

ሀገር አቀፍ

ክልላዊ

1

የኦሮሞ ብሔራዊ ኮንግረስ

ኦብኮ


*

2

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት

መኢአድ

*


3

የምዕራብ ሶማሌ ዲሞክራቲክ ፓርቲ

ምሶዲፓ


*

4

የኦሮሞ ነጻነት አንድነት ግንባር

ኦነአግ


*

5

የጋሞ ዴሞክራሲያዊ ኅብረት

ጋዴህ


*

6

የሐረሪ ብሔራዊ ሊግ

ሐብሊ


*

7

የኢትዮጵያ የሠላምና የዴሞክራሲ ፓርቲ

ኢሰዴፓ

*


8

የቤንሻንጉልና ጉሙዝ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ

ቤጉሕዴፓ


*

9

የሶማሌ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ

ሶሕዴፓ


*

1ዐ

የኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ፓርቲ

ኢዴፓ

*


11

የትግሪ ወርጂ ብሔረሰብ ዲሞክራሲያዊ አንድነት ፓርቲ

ትወብድአፓ


*

12

የመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት

መአሕድ

*


13

 

የኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲ

ኢሶዲፓ

*


14

የሐረሪ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ

ሐሕዴፓ


*

15

የኢትዮጵያዊያን አንድነት ዴሞክራሲያዊ ድርጅት

ኢአዴድ


*

16

የደንጣ፣ ዱባሞ ክችንችላ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት

ደዱክሕዴድ


*

17

የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ሕብረት

ደኢሕዴህ


*

18

የሐድያ ብሔር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት

ሐብዴድ


*

19

የከምባታ ሕዝቦች ኮንግረስ

ከሕኮ


*

2ዐ

የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ

ደኢሕዴን


*

21

የጌዴኦ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት

ጌሕዴድ


*

22

የሶማሌ ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች ቅንጅት

ሶዴኃቅ


*

23

የኦሮሞ አቦ ነጻነት ግንባር

ኦአነግ


*

24

የየም ብሔረሰብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ

የብዴን


*

25

የአፋር ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ

አብዴፓ


*

26

የኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት

ኦሕዴድ


*

27

ብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ

ብአዴን


*

28

የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር

ኢሕአዴግ

*


29

 

ሕዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ

ሕወሐት


*

3ዐ

የጠምባሮ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ሕብረት

ጠሕዴሕ


*

31

የባሕር ወርቅ መስመስ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት

ባወመሕዴድ


*

32

የጉራጌ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር

ጉሕዴግ


*

33

ሶዶ ጐርደና ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት

ሶጐሕዴድ


*

34

የኦሮሚያ ነጻነት ብሔራዊ ፓርቲ

ኦነብፓ


*

35

የኢትዮጵያ ሱማሌ ልማትና ዲሞክራሲ ፓርቲ

ኢሱልማዲፓ


*

36

የኮንሶ ሕዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ኅብረት

ኮሕዴኅ


*

37

የኦሞ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ኅብረት

ኦሕዲኅ


*

38

የሲዳማ አርነት ንቅናቄ

ሲኦን


*

39

የዶንጋ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት

ዶህዴድ


*

4ዐ

የወላይታ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር

ወሕዴግ


*

41

ገዳ ሥርዓት አራማጅ ፓርቲ

ገስአፓ

*


42

ዱቤና ደገኒ ብሔረሰብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ

ዱደብዴፓ


*

43

የኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ሕብረት

ኢዴሕ

*


44

የዲል ወቢ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ

ዲወሕዴን


*

45

የአፋር አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት ግንባር

አርዱፍ


*

46

መላው ኢትዮጵያዊያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ

መኢዴፓ

*


47

የኢትዮጵያዊ ፓን አፍሪካኒስት ፓርቲ

ኢፓአፓ

*


48

የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች ኅብረት

ኢዴኃሕ

*


49

የኦሮሞ ፌዴራሊስት ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ

ኦፌዴን

*


5ዐ

የሲዳማ ሀዲቾ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት

ሲሀሕዲድ


*

51

የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ

ኢብአፓ

*


52

የደቡብ ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ኃይሎች አንድነት

ደኢዲኃአ


*

53

የአፋር ነጻ አውጪ ግንባር ፓርቲ

አነአግፓ


*

54

የመላው ኢትዮጵያዊያን ብሔራዊ ንቅናቄ

መኢብን

*


55

የቤንች ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት

ቤሕዲድ


*

56

የአፋር ብሔራዊ አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባር

አብአዲግ


*

57

የኦሮሞ ነጻነት ፓርቲ

ኦነፓ


*

58

ቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ - ቅንጅት

ቅንጅት

*


59

የሸኮና አካባቢው ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት

ሸአሕዲድ


*

6ዐ

የሀዲያ ብሔራዊ አንድነት ዲሞክራሲያዊ ድርጅት

ሀብአዲድ


*

61

የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ አንድነት ንቅናቄ

ኢዲአን

*


62

የኦሮሞ ሕዝብ ኮንግረስ

ኦሕኮ


*

63

ዓረና ትግራይ ለዲሞክራሲ ሉዓላዊነት

ዓረና


*

64

ብርሃን ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ

ብአዴፓ

*


65

ወለንኛ ቋንቋ ተናጋሪ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ

ወቋተሕዴን

*


66

የኢትዮጵያ አዲስ ምዕራፍ ፓርቲ

አዲስ ምዕራፍ


*

67

የአርጎባ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት

አሕዲድ


*

68

የሐረሪ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት

ሐዲድ


*

69

የጋምቤላ ሕዝቦች አንድነት ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ

ጋሕአዲን


*

7ዐ

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ አንድነት

አንድነት

*


71

የኢትዮጵያ ፍትህና ዲሞክራሲያዊ ኃይሎች ግንባር

ኢፍዲኃግ

*


72

የመላው ኦሮሞ ህዝብ ዲሞክራቲክ ፓርቲ

መኦህዲፓ

*


73

የአርጐባ ብሔረሰብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ

አብዴን


*

74

የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ

ኢራፓ

*


75

የማኦ-ኮሞ ልዩ ወረዳ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ አንድነት ንቅናቄ

ማኮልወህዴአን


*

76

የጋሞ ጐፋ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ አንድነት

ጋጐህዴአ


*

 

 

ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ህጋዊ ዕውቅና ላላቸው ሀገር አቀፍ እና የክልል

የፖለቲካ ፓርቲዎች የተላለፈ

የስብሳባ ጥሪ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከኦሮሚያ እና ከደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልሎች ቀደም ሲል የአካባቢ ምርጫ ባልተካሄደባቸው አንዳንድ ወረዳዎችና ቀበሌዎች ላይ ምርጫ እንዲካሄድ ያቀረቡትን ጥያቄና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ከከተማው አስተዳደር ምክር ቤት፣ ከክፍለ ከተማ ምክር ቤቶች እና ከቀበሌ ምክር ቤቶች በተለያዩ ምክንያቶች የተጓደሉ የምክር ቤት አባላትን በሕጉ መሠረት በማሟያ ምርጫ እንዲሟሉ ለቦርዱ ያቀረቡትን ጥያቄ ታህሣሥ 15 ቀን 2ዐዐ3 ዓ.ም. ባካሄደው ዐዐ7/ዐ3 መደበኛ ስብሰባው መርምሮ ማሟያ ምርጫው እንዲካሄድ ውሣኔ ሰጥቷል፡፡

ቦርዱ በህጉ መሠረት ማሟያ ምርጫውን በሦስት ወራት ጊዜ ውስጥ ለማስፈፀም እንዲቻል ረቂቅ የምርጫ አፈፃፀም የጊዜ ሠሌዳ አዘጋጅቷል፡፡ ይህንኑ ረቂቅ የጊዜ ሠሌዳ ተግባራዊ ከማድረጉ በፊት በማሟያ ምርጫው ከሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ተገቢውን ምክክር ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ አግኝቶታል፡፡

በመሆኑም በምርጫው የምትወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ረቡዕ ታኀሣሥ 2ዐ ቀን 20ዐ3 ዓ.ም. ከጠዋቱ በ3፡ዐዐ ሰዓት በፓርቲው የተወከሉ አንድ ከፍተኛ አመራር በቦርዱ ዋና ጽሕፈት ቤት የመሰብሰባቢያ አዳራሽ እንዲገኙ እንድታደርጉልን ቦርዱ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

አዲስ አበባ

 

ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጽ/ቤት የ2002 ጠቅላላ ምርጫ

አፈፃፀም ሂደትን ለመገምገም የሚያስችል የዳሰሳ ጥናት መጀመሩን

አስመልክቶ የተሠጠ ፕሬስ ማብራሪያ


የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ2ዐዐ2 ዓ.ም. ጠቅላላ ምርጫን በእቅዱ መሠረት ከመቸውም ጊዜ በላቀ የሕዝብ ተሳትፎ፣ በተሳካና ሰላማዊ በሆነ መልኩ ማካሄዱ ይታወሳል፡፡

ቦርዱ ይህን ምርጫ ለማሳካት የቻለው ለምርጫው የሚያግዙ ደንብና መመሪያዎችን ከሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በመመካከርና በማዘጋጀት አገልግሎት ላይ እንዲውሉ በማድረጉ፣ ለሁሉም ባለድርሻ አካላት በቂ ሥልጠና በመስጠቱ፣ ለመራጮች የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት መስጫ ሰነድ አዘጋጅቶ ትምህርቱ በሁሉም የመገናኛ ብዙሃን በተከታታይ እንዲተላለፍ በማድረጉና የምርጫ ቁሳቁሶችን በበቂ መጠን በማዘጋጀትና በወቅቱ እስከ ምርጫ ጣቢያ ማድረስ በመቻሉ ነው፡፡

በአንድ ሀገር ምርጫ ከተጠናቀቀ በኋላ የምርጫ አፈፃፀም ሂደቱን መገምገም እና ከግምገማው የተገኘውን ውጤት በመቀመር ለቀጣይ ምርጫ በተሻለ መልኩ ለመዘጋጀት እንዲያስችል በግብዓትነት መጠቀም ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው አሠራር ነው፡፡

ስለሆነም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ አፈፃፀም ብቃቱን ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል፣ የ2ዐዐ2 ጠቅላላ ምርጫ አፈፃፀም ሂደትን ለመገምገም የሚያስችል የዳሰሳ ጥናት ማካሄድ በምርጫ ሂደት የታዩ ጠንካራ ጐኖችን ፈትሾ ይበልጥ ለማጐልበትና ጉድለቶች ካሉም ለማስተካከል በ2ዐዐ3 በጀት ዓመቱ በዕቅድ ከያዛቸው ቁልፍ ተግባራት በዋነኛነት የሚጠቀስ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪም፡-

1. የምርጫ ክልሎችን በአዲስ መልክ የማካለል ሥራ ለመሥራት ዝግጅት ማድረግ፣

2. በ2ዐዐዐ ዓ.ም በተለያየ ምክንያት የአካባቢ ምርጫ ባልተካሄደባቸው የተወሰኑ ቀበሌዎች የአካባቢ ምርጫ ማካሄድና ከዚሁ ጋር በተያያዘ አዲስ አበባ ከተማን ጨምሮ በተለያዩ ምክንያቶች የተጓደሉ የምክር ቤት አባላት ካሉ በሚቀርብ ጥያቄ መሠረት የማሟያ ምርጫ ማካሄድ

የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

ቦርዱ በበጀት ዓመቱ አንደኛና ሁለትኛ ሩብ ዓመት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ የሚሰራው የ2ዐዐ2 ጠቅላላ ምርጫ አፈፃፀም ሂደትን ተቀባይነት ባለው አሠራር ለመገምገም የሚያስችል የዳሰሳ ጥናት ማካሄድ ይሆናል፡፡

የዳሰሳ ጥናቱ ዓላማ፡-

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ2ዐዐ2 ዓ.ም. ያካሄደውን ጠቅላላ ምርጫ አፈፃፀም ተቀባይነት ባለው አሠራር በማጥናት፣ ጠንካራና ደካማ ጐኖችን ለይቶ ከጥናቱ የተገኘውን ውጤት በቀጣይ በግብዓትነት በመጠቀም የተጀመረውን በአገራችን የዲሞክራሲ ሂደት አጠናክሮ ማስቀጠል ነው፡፡

ለዚህ ዓላማ መሳካት ይረዳ ዘንድ በአሁኑ ጊዜ ቅድመ ዝግጅት የተደረገ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ፡-

- የቦርድ አባላት ከየክልሉ መስተዳድር አካላት ጋር በመነጋገር ለጥናቱ ምቹ ሁኔታዎችን ፈጥረዋል፡፡

- ለጥናቱ አስፈላጊ መጠይቆች /Questionnaires/ በቦርዱ ተዘጋጅተው አግባብነት ባለው ባለሙያ አማካሪነት እንዲታይ ከመደረጉም በተጨማሪ የጥናቱ ሥልት እንዲለይና እንዲወሰን ተደርጓል፡፡

- ለጥናቱ ግብዓት የሚሆኑ መጠይቆችን ከየክልሉ አስሞልተውና አሰባስበው የሚያመጡ የጽ/ቤቱ ባለሙያዎችና የየክልሉ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊዎችን በመመደብ ለ 2 ቀናት በማዕከል ደረጃ ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡

- በጥናቱ ሂደት የቦርድ አባላት በየክልሉ በመንቀሳቀስ የሚጋጥሙ ችግሮችን መፍትሄ ለመስጠት ዝግጁ ሆነው ይገኛሉ፡፡

ዳሰሳ ጥናቱ የሚያካትታቸው ባለድርሻ አካላት፡-

1. መራጩ ህዝብ

2. የፖለቲካ ፓርቲዎች

3. የህዝብ ታዛቢዎች

4. የምርጫ አስፈፃሚዎች

5. የመገናኛ ብዙሃን

6. የሲቪክ ማህበራት

7. የፍትህ አካላት እና

8. የአስተደደር አካላት ናቸው፡፡

በአጠቃላይ ጥናቱ በአገር አቀፍ ደረጃ በዋነኛነት ትኩረት የሚያደርገው በመራጩ ህዝብ ላይ ሲሆን በዚሁ መሠረት፡-

- በሁሉም የክልል መስተዳደሮች እና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች

- በ77 የዞን መስተዳድሮች

- ለናሙና በተመረጡ 154 የምርጫ ክልሎች

- ለናሙና በተመረጡ 916 የምርጫ ጣቢያዎች ከእያንዳንዱ የምርጫ ጣቢያ 15 መራጮች ናሙና/ Sam*le/ ተወስዶ በጠቅላላው 13,74ዐ መራጮች በጥናቱ ይካተታሉ፡፡

ሁሉም ባለድርሻ አካላት በጥናቱ የሚካተቱ ሲሆን በተያዘው ዕቅድ መሠረት ይከናወናል፡፡

ከዳሰሳ ጥናቱ የሚጠበቅ ውጤት ፡-

1. የባለድርሻ አካላትን በምርጫ አፈፃፀም ሂደት፣ በሕግ ማቀፍና በአሠራር ማሻሻያ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ዙሪያ ያላቸውን አስተያየት መለየት፣

2. እስከ ታችኛው እርከን ድረስ ባለው የምርጫ አፈፃፀም ሂደት ውስጥ ያሉ ጠንካራና ደካማ ጉኖችን መለየትና የመፍትሄ አቅጣጫ ማስቀመጥ ናቸው፡፡

ዳሰሳ ጥናቱ የሚወስደው ጊዜ፡-

መረጃ የመሰብሰቡ ሥራ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ በዕቅድ ተይዟል፡፡ የጥናት ቡድኖች በሁሉም የአገራችን ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች ከጥቅምት 29 ቀን 2ዐዐ3 ዓ.ም. ጀምሮ ተሰማርተዋል፡፡

ይህ ጥናት ከተጠናቀቀ በኋላ ቦርዱ የጥናቱን ጠቅላላ ውጤት ሪፖርት አዘጋጅቶ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሚያቀርብ ይሆናል፡፡

በመጨረሻም ጥናቱ ስኬታማ እንዲሆን በመስክ ከተሰማሩት ቡድኖች በተጨማሪ ህብረተሰቡና በየደረጃው የሚገኙ የመስተዳደር አካላት እንዲሁም የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት የጥናቱን ፋይዳ ተገንዝበው ተገቢውን ድጋፍና ትብብር በማድረግ የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ ቦርዱ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

 

 

 

ኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጽ/ቤት

ህዳር 4/2003 ዓ.ም.

አዲስ አበባ


ግንቦት 15 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. በመላው ሀገሪቱ የተካሄደው አራተኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ ውጤት


በ2002 ዓ.ም ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በተካሄደው አገር አቀፍ ምርጫ ዕጩዎች ያገኙት ጠቅላላ ድምፅ


በ2002 ዓ.ም በተካሄደው አገር አቀፍ የክልል ምክር ቤት አባላት ምርጫ ዕጩዎች ያገኙት ጠቅላላ ድምፅ

 


 

 

በኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ

ፀድቆ ይፋ የተደረገ ግንቦት 15 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. የተካሄደው

ጠቅላላ ምርጫ ውጤት

የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ግንቦት 15 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. በመላው ሀገሪቱ አራተኛውን ዙር ጠቅላላ ምርጫ ለማስፈፀም ባወጣው የምርጫ አፈፃፀም የጊዜ ሠሌዳ መሠረት ምርጫው የተረጋጋ፣ ቀልጣፋ፣ ነፃ፣ ፍትሃዊ፣ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊና የሕዝብ አመኔታ በተረጋገጠበት መልኩ ተጠናቋል፡፡

 

የምርጫው አጠቃላይ ውጤት ሰኔ 14 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. በቦርዱ ፀድቆ ለሕዝብ ይፋ እንደሚደረግ ቀድሞ በወጣው የምርጫ አፈፃፀም የጊዜ ሠሌዳ ተገልጿል፡፡

 

በተሻሻለው የምርጫ ሕግ አዋጅ ቁጥር 532/1999 ዓ.ም አንቀፅ 76 ንዑስ አንቀፅ 5 መሠረት ቦርዱ በአጠቃላይ የምርጫው ውጤት ከየምርጫ ክልሉ ተጠናቆ እስከሚደርሰው ድረስ ከግንቦት 16 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. ጀምሮ ከየምርጫ ክልሉ የመጣለትን፣

  1. የ547 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ምርጫ ጊዜያዊ ውጤት፣
  2. የ9ኙን ክልሎች የክልል ምክር ቤቶች አባላት ምርጫ ጊዜያዊ ውጤት፣

ግንቦት 16፣ 17 እና 19 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. በቦርዱ ጽሕፈት ቤት ለሀገር ውስጥና ለውጪ የመገናኛ ብዙሃን ይፋ አድርጓል፡፡

ቦርዱ ሰኔ 11 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. ባካሄደው 149ኛ አስቸኳይ ስብሰባው፣

- ግንቦት 15 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. በመላው ሀገሪቱ የተካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት ከየምርጫ ክልሉ ተጠቃሎ ለቦርዱ መድረሱን፣

- በአሁኑ ጊዜ ህጉን ተከትሎ ለቦርዱ ቀርቦ ውሣኔ ያላገኘ አቤቱታ አለመኖሩን በማረጋገጥና ውጤቱን በጥልቀት መርምሮ በማፅደቅ ለሕዝብ ይፋ እንዲሆን ወስኗል፡፡

በመሆኑም ግንቦት 15 ቀን በመላው ሀገሪቱ የተካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት ከዚህ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

 

1ኛ/ በምርጫው 63 የፖለቲካ ድርጅቶች ተሳትፈው

 

1.1 ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ ወንድ 1,916 (87.6%) ሴት 272 (12.4%)

በጠቅላላም 2,188 ዕጩዎችን፣

 

1.2 ለክልል ምክር ቤት ምርጫ ወንድ 4,ዐ21(84.7%) ሴት 725 ( 15.3%)

በጠቅላላው 4,746 ዕጩዎችን

 

1.3 በግል

  • ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ ወንድ 33 (97.1%) ሴት 1(2.9%) በጠቅላላው 34 ዕጩዎችን
  • ለክልል ምክር ቤት ምርጫ ወንድ 9 (81.8%) ሴት 2 (18.1%) በጠቅላላ 11 ዕጩዎችን፣ በጠቅላላው ወንድ 5,979 (85.7%) ሴት 1,ዐዐዐ (14.3%) በጠቅላላው 6,979 ዕጩዎች በማቅረብ ተወዳድረዋል፡፡

 

2ኛ/ ለመምረጥ የተመዘገበው ሕዝብ ወንድ 16,674,280 (52.2%) ሴት 15,252,24ዐ (47.8%) በድምሩ 31,926,52ዐ ነው፡፡

3ኛ/ ድምፅ የሰጠው ሕዝብ ወንድ 15,617,453 (52.4%) ሴት 14,214,737 (47.6%) በድምሩ 29,832,19ዐ ነው፡፡

4ኛ/ ከተመዘገበው ውስጥ ድምፅ የሰጠ መራጭ 93.4 በመቶ ነው፡፡ ከተመዘገበው ውስጥ ድምፅ ያልሰጠው መራጭ 6.6 በመቶ ነው፡፡

 

1. የጠቅላላ ምርጫ ውጤት

1.1 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ምርጫ ውጤት

 

በጠቅላላው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ ከተካሄደባቸው 547 የምርጫ ክልሎች ውስጥ፣

  • የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) 499 መቀመጫዎች፣
  • የአፋር ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አብዴፓ) 8 መቀመጫዎች፣
  • የሶማሌ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ሶሕዴፓ) 24 መቀመጫዎች፣
  • የቤንሻንጉል ጉሙዝ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ቤጉሕዴፓ) 9 መቀመጫዎች፣
  • የጋምቤላ ህዝቦች አንድነት ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጋህአዴን) 3 መቀመጫዎች፣
  • የሐረሪ ብሔራዊ ሊግ (ሐብሊ) 1 መቀመጫ፣
  • የአርጎባ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (አህዴድ) 1 መቀመጫ፣
  • የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) 1 መቀመጫ፣
  • በግል 1 መቀመጫ፣

አሸንፈዋል፡፡

2. የክልል ምክር ቤት አባላት ምርጫ ውጤት

በመላው ሀገሪቱ በ9 ክልል ምክር ቤቶች ምርጫ ተካሂዷል፡፡ ውጤቱም ከዚህ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

 

2.1 ትግራይ

የትግራይ ክልል ምክር ቤት 152 መቀመጫዎች አለው፡፡

  • ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት-ኢህአዴግ) 152 መቀመጫዎች አሸንፏል፡፡

 

2.2. አፋር

የአፋር ክልል ምክር ቤት 96 መቀመጫዎች አለው፡፡

  • የአፋር ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አብዴፓ) 93 መቀመጫዎች፣
  • የአርጎባ ህዝብ ዴምክራሲያዊ ድርጅት (አህዴድ) 3 መቀመጫዎች አሸንፏል፡፡

 

2.3. አማራ

የአማራ ክልል ምክር ቤት 294 መቀመጫዎች አለው፡፡

  • ብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ብአዴን-ኢህአዴግ) 294 መቀመጫዎች አሸንፏል

 

2.4. ኦሮሚያ

የኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት 537 መቀመጫዎች አለው፡፡

  • የኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦህዴድ-ኢህአዴግ) 537 መቀመጫዎች አሸንፏል፡፡

2.5. ሶማሌ

የሶማሌ ክልል ምክር ቤት 186 መቀመጫዎች አለው፡፡

  • የሶማሌ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ( ሶህዴፓ) 186 መቀመጫዎች አሸንፏል፡፡

2.6 ቤንሻንጉል ጉሙዝ

የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት 99 መቀመጫዎች አለው፡፡

  • የቤንሻንጉል ጉሙዝ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ቤጉሕዴፓ) 98 መቀመጫዎች፣
  • የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) 1 መቀመጫ አሸንፏል፡፡

 

2.7. የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች

  • የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ምክር ቤት 348 መቀመጫዎች አለው፡፡
  • የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢህዴን-ኢህአዴግ) 348 መቀመጫዎች አሸንፏል፡፡

2.8. የጋምቤላ ሕዝቦች

የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት 156 መቀመጫዎች አለው፡፡

  • የጋምቤላ ሕዝቦች አንድነት ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጋሕአዴን) 156 መቀመጫዎች አሸንፏል፡፡

2.9. የሐረሪ ሕዝብ

የሐረሪ ሕዝብ ክልል ምክር ቤት 36 መቀመጫዎች አለው፡፡

  • የሐረሪ ብሔራዊ ሊግ (ሐብሊ) 18 መቀመጫዎች፣
  • የኦሮሞ ሕዝብ ዴሞከራሲያዊ ድርጅት (ኦህዴድ-ኢህአዴግ) 18 መቀመጫዎች አሸንፈዋል፡፡

 

3. ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለክልል ምክር ቤቶች የአሸናፊ የፖለቲካ ድርጅቶችና ዕጩዎች ዝርዝርና ያገኙት ድምፅ በቦርዱ ጽሕፈት ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ቦርዱ ጥቅምት 24 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. ባወጣው የምርጫ አፈፃፀም የጊዜ ሠሌዳ መሠረት ዛሬ ሰኔ 14 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. ለሕዝብ እነሆ ይፋ ተደርጓል፡፡ ይኸው ዝርዝር በተከታታይ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ይወጣል፡፡ በተጨማሪም በቦርዱ ድህረ ገፅ ዛሬ ተጭኗል፡፡

 

 

4. በተመሳሳይ ሁኔታ ለጠቅላላ ምርጫ በእያንዳንዱ የምርጫ ክልል የተወዳደሩ የፖለቲካ ድርጅቶች ዕጩዎች ያገኙት ድምፅ ዝርዝር ይፋ ተደርጓል፡፡

 

 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ሰኔ 14 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም.

አዲስ አበባ

 

 

 

II. ግንቦት 22 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. በሶማሌ ክልል የተካሄደው የአካባቢ ምርጫ ውጤት

ቦርዱ በልዩ ሁኔታ የካቲት 24 ቀን በ2ዐዐ2 ዓ.ም. ባወጣው የምርጫ አፈፃፀም የጊዜ ሠሌዳ መሠረት በሶማሌ ክልል ግንቦት 22 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. የአካባቢ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሀዊ፣ ሠላማዊ ዴሞክራሲያዊና የሕዝብ አመኔታን ባተረፈ መልኩ መከናወኑን አረጋግጧል፡፡

በዚሁ መሠረት ቦርዱ በክልሉ የተካሄደውን የአካባቢ ምርጫ ውጤት መርምሮ እና አፅድቆ ሰኔ 14 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. ይፋ እንዲሆን በወሰነው መሠረት ከዚህ እንደሚከተለው እንገልፃለን፡፡

1. የጅጅጋ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት አባላት ምርጫ ውጤት

  • የሶማሌ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ሶህዴፓ) በ13 ቀበሌዎች ውስጥ የሚገኙትን 75 መቀመጫዎች አሸንፏል፡፡ ከዚህ ውስጥ ወንድ 51 (68%) ሴት 24 (32%) ናቸው፡፡

2. የወረዳ ምክር ቤት አባላት ምርጫ ውጤት

  • የሶማሌ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ሶህዴፓ) በ52ቱም ወረዳዎች ውስጥ የሚገኙትን 4,032 መቀመጫዎች አሸንፏል፡፡ ከዚህ ውስጥ ወንድ 3,412 (84.6%) ሴት 620 (15.4%) ናቸው፡፡

 

3. የቀበሌ ምክር ቤት አባላት ምርጫ ውጤት

  • የሶማሌ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ሶህዴፓ) በ7ዐ6 ቀበሌዎች ውስጥ የሚገኙትን 47,849 መቀመጫዎች አሸንፏል፡፡ ከዚህ ውስጥ ወንድ 37,541 (78.5%) ሴት 10,308 (21.5%) ናቸው፡፡

የሶማሌ ክልል የአካባቢ ምርጫ ውጤት ዝርዝርም በቦርዱ ጽሕፈት ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ዛሬ ሰኔ 14 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. ይፋ ተደርጓል፡፡

 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ሰኔ 14 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም.

አዲስ አበባ

 

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፀደቀ

ግንቦት 15 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. በመላው ሀገሪቱ የተካሄደው አራተኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ

የክልል ምክር ቤቶች አጠቃላይ ውጤት

ዘጠኝ ክልሎች በድምሩ 1,9ዐ4 የክልል ምክር ቤቶች መቀመጫዎች አላቸው፡፡

 

 

ተ.ቁ.

ክልል

የክልል ምክር ቤት መቀመጫ ብዛት

አሸናፊ ፓርቲ

ያገኙት መቀመጫ

1

ትግራይ

152

ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ /ሕወሓት - ኢሕአዴግ/

152

2

አፋር

96

የአፋር ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ /አብዴፓ/

93

የአርጎባ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት /አሕዴድ/

3

3

አማራ

294

ብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ/ብአዴን - ኢሕአዴግ/

294

4

ኦሮሚያ

537

የኦሮሞ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት /ኦሕዴድ - ኢሕአዴግ/

537

5

ሶማሌ

186

የሶማሌ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ /ሶሕዴፓ/

186

6

ቤንሻንጉል ጉሙዝ

99

የቤንሻንጉል ጉሙዝ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ /ቤጉሕዴፓ/

98

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት /መኢአድ/

1

7

የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች

348

የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ደኢሕዴን - ኢሕአዴግ/

348

8

ጋምቤላ

156

የጋምቤላ ሕዝቦች አንድነት ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ጋሕአዴን/

156

9

ሐረሪ

36

የሐረሪ ብሔራዊ ሊግ /ሐብሊ/

18

የኦሮሞ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት /ኦሕዴድ - ኢሕአዴግ/

18




ያሸነፉት መቀመጫ ብዛት ድምር

1,9ዐ4

 

 

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፀደቀ

ግንቦት 15 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. በመላው ሀገሪቱ የተካሄደው አራተኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አጠቃላይ ውጤት

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 547 መቀመጫዎች አሉት፡፡

 

 

ተ.ቁ.

አሸናፊ ፓርቲ

ያገኙት መቀመጫ

1

የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር /ኢሕአዴግ/

499

2

የሶማሌ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ /ሶሕዴፓ/

24

3

የቤንሻንጉል ጉሙዝ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ /ቤጉሕዴፓ/

9

4

የአፋር ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ /አብዴፓ/

8

5

የጋምቤላ ሕዝቦች አንድነት ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ጋሕአዴን/

3

6

የሐረሪ ብሔራዊ ሊግ /ሐብሊ/

1

7

የአርጎባ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት /አሕዴድ/

1

8

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ /መድረክ/

1

9

በግል

1


ያሸነፉት መቀመጫ ብዛት ድምር

547

 

 

 

 

 

prev
next

ለፖለቲካ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል፡፡

ታህሳስ 3 ቀን 2004 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለፖለቲካ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ደብረዘይት በሚገኘው የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት ከታህሳስ 2-6 ቀን 2004 ዓ.ም ጀምሮ ለ5 ቀናት በሚቆይ በሁለንተናዊ ለውጥ አመራር (Transformational Leadership) ሥልጠና  በመሰጠት ላይ ይገኛል፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች አቅም ለመገንባት በሀገራችን የተጀመረውን የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ሂደት በይበልጥ ለማጠናከር እና ወደ ተሻለ ...

ሙሉ ዜና

ቦርዱ ከሲቪክ ማህበራት ጋር የመራጮችና የሥነ-ዜጋ ትምህርት አስ

ህዳር 23 ቀን 2004 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለኢትዮጵያ ለሴቶች ፌዴሬሽን፣ለኢትዮጵያ መምህራን ማህበር እና ለአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር  ህዳር  21 ቀን 2004 ዓ.ም የአሰልጣኞች ሥልጠና በአዳማ ከተማ መስጠቱን አስታወቀ፡፡ ቦርዱ በተሻሻለው የምርጫ ህግ አዋጅ ቁጥር 532/1999 መሰረት መራጩ ህዝብ ስለምርጫ በቂ ግንዘቤ እንዲያገኝ ለማስቻል የመራጮችና የሥነ- ዜጋ ትምህርትን የተለያዩ ዘዴዎችን ...

ሙሉ ዜና

ቦርዱ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር የጋር ምክክር አደረገ

ህዳር 21 ቀን 2004 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከፖሊቲካ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በተሻሻለው የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 573/2000 ዓ.ም የጋር ምክክር መድረክ  በአዳማ  ከተማ አካሄደ። የቦርዱ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር መርጋ በቃና  በምክክር መድረኩ ላይ አንደገለፁት ቦርዱ ባለፉት ሁለት አሥርት አመታት የጠቅላላ ፣ የአካባቢ፣ የማሟያ ፣ የድጋሚ ምርጫ እና የህዝብ ውሳኔዎችን ...

ሙሉ ዜና
 

አዳዲስ ዝግጅቶች

ለጊዜው ምንም ዝግጅት አልተገኘም
 


ኮፒራይት © 2010
የኢትዮጵያ ብሔራዌ ምርጫ ቦርድ