ቌንቌ | Language
     
 
መግቢያ
     
 
Banner

የካቲት 20 ቀን 2003 ዓ.ም የማሟያ ምርጫ

3:30

የካቲት 20 ቀን 2003 ዓ.ም የማሟያ ምርጫ

3:45

የካቲት 20 ቀን 2003 ዓ.ም የማሟያ ምርጫ

3:50

የካቲት 20 ቀን 2003 ዓ.ም የማሟያ ምርጫ

4:00

የካቲት 20 ቀን 2003 ዓ.ም የማሟያ ምርጫ

 

የመራጮች እና የስነዜጋ ትምህርት በየክልሉ የሬዲዮ የመገናኛ ብዙኃን

ከጥቅምት 1 ቀን 2ዐዐ4 ዓ.ም. ጀምሮ መሠራጨቱን በተመለከተ

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጠ መግለጫ

 

በተሻሻለው የምርጫ ህግ አዋጅ ቁጥር 532/1999 ዓ.ም. አንቀጽ 89 እንደተደነገገው፤

-     ቦርዱ የተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎችን በመጠቀም መራጩ ስለምርጫው በቂ ግንዛቤ የሚያገኝበት ስልት በመቀየስ የመራጮች እና የስነዜጋ ትምህርት ይሰጣል፣

 

-     ቦርዱ የመራጮች እና የስነዜጋ ትምህርት በሌላ ድርጅት መስጠት አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው የማስተማር ፈቃድ ሊሰጥ ይችላል፣

 

-     ቦርዱ አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው አግባብ ካለው አካል ጋር በመዋዋል የመራጮችና የስነዜጋ ትምህርት እንዲሰጥ ሊያደርግ ይችላል፡፡

 

በዚሁ መሠረት ቦርዱ ቀደም ባሉ ምርጫዎች ሲሰጥ የነበረው የመራጮችና የስነዜጋ ትምህርት ወጥነት እና ተከታታይነት የሌለው እንደነበር በማረጋገጥ ይህንኑ ችግር ለመቅረፍ የሚያስችል የማስተማሪያ ሰነድ አዘጋጅቶ በ2ዐዐ2 ዓ.ም. ጠቅላላ ምርጫ ተግባራዊ አድርጓል፡፡

ሰነዱ በወቅቱ ቦርዱ ባዘጋጃቸው የተለያዩ አውደጥናቶች ላይ በመስኩ ባለሙያዎች በጥልቀትና በስፋት ተገምግሟል፡፡ በመሆኑም ጥሩ ግብአት አግኝቷል፡፡ በዚሁ መሠረት ቦርዱ በ2ዐዐ2 ዓ.ም. በተካሄደው ጠቅላላ ምርጫ የማስተማሪያ ሰነዱ በመገናኛ ብዙኃንና በተለያዩ የትምህርት መስጫ ዘዴዎች ለመራጩ ሕዝብ ተገቢውን የምርጫ አፈፃፀም መረጃ እንዲደረስ አድርጓል፡፡ ስለሆነም ሰነዱ ለምርጫው ስኬታማነት ከፍ ያለ አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡

ቦርዱ በ2ዐዐ2 ዓ.ም. የሰነዱ ትግበራ ላይ ያገኛቸውን ተሞክሮዎችን፣ በሀገር ውስጥ እና በውጪ አውደ ጥናቶች ላይ በተለያዩ ጊዜያት የቀሰማቸውን ልምዶችና ተሞክሮዎች፣  ከበርካታ ተቋማትና ባለሙያዎች በቂ ግብዓት ከአገኘ በኋላ ሰነዱን ወደ ማኑዋል/መጽሐፍ ለውጦታል፡፡

ማኑዋሉ በአማርኛ  እና በተለያዩ የክልል የሥራ ቋንቋዎች ማለትም በትግርኛ፣ በአፋርኛ፣ በኦሮምኛ፣ እና በሶማሊኛ ቋንቋዎች ተተርጉሞ በህትመት ላይ ይገኛል ፡፡ በተጨማሪም በደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ክልል በስፋት ከሚነገሩ እና በዩኒቨርስቲ አና በኰሌጅ ደረጃ ትምህርት በሚሰጥባቸው በሲዳምኛ፣ በሀድይኛ፣ በወላይትኛ፣ በጋሞኛ እና በከፊቾ ቋንቋዎች ትርጉሙ እየተጠናቀቀ ይገኛል፡፡ በመሆኑም በቅርብ ቀን ውስጥ ወደ ህትመት ይገባል ተብሎ የታመናል፡፡ በተጨማሪም በሐረሪ ቋንቋ ለማስተርጐም በሂደት ላይ እንገኛለን፡፡ በቀጣይም በተጨማሪ በሌሎች የሀገሪቱ ቋንቋዎች ደረጃ በደረጃ ተተርጉሞ ለመራጩ ሕዝብ የሚደርስበት ሁኔታ ይመቻቻል፡፡

በአሁኑ ጊዜ ይህን ማኑዋል በመጠቀም የመራጮችና የስነዜጋ ትምህርትን ለየክልሉ ሕዝብ በተገቢው ሁኔታ ለማድረስ በየክልሉ የመገናኛ ብዙኃን አማካይነት በሬዲዮ በስፋት እንዲሰራጭ የአየር ሰዓት ግዢ እና የሥርጭት ውል በቦርዱ ጽ/ቤት ተፈፅሟል፡፡ በተጨማሪም ከኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት እና ከፋና ብሮድካትስ ኮርፖሬት ጋር የመራጮችና የስነዜጋ ትምህርት በሬዲዮ ለአንድ ዓመት ለመስጠት የሚያስችል የውል ስምምነት ፈጽሟል፡፡

በዚህ ረገድ የትምህርቱ አሰጣጥ ዘዴ ወጥነት እንዲኖረው ከፌዴራልና ከክልል መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ጋር የጋራ ምክክርና ውይይት ተካሂዷል፡፡ ለዚህም የሥራ ቅልጥፍና የመራጮችና የስነዜጋ ትምህርቱን ተግባራዊ ለማድረግ የቦርዱ እና የጽሕፈት ቤቱ አመራር ከሁሉም ክልል መንግሥታት ርዕሰ መስተዳድሮች ጋር በመመካከር ስኬታማ እና ቀጣይነት ባለው መልኩ እንዲሰጥ ሁኔታዎችን አመቻችቷል፡፡

ስለሆነም መላው የሀገራችን ህዝቦች ከጥቅምት 1 ቀን 2ዐዐ4 ዓ.ም. ጀምሮ በቀጣይነት ከላይ በተጠቀሱት የክልል የመገናኛ ብዙኃን እና ሬዲዮ ጣቢያ የሚተላለፈውን የመራጮች እና የስነዜጋ ትምህርት በንቃት እንድትከታተሉት፣ ንቁ ተሳትፎ እንድታደርጉ እና ገንቢ አስተያየት እንድትሰጡበት ቦርዱ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ በተጨማሪም ይህንኑ ለማጠናከር በስርጭት ረገድ በስፋት ተደማጭ በሆኑት የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት እና የሬዲዮ ፋና ብሮድካስት ኮርፖሬት አማካይነት ትምህርቱ በሀገሪቱ ዋና ዋና ቋንቋዎች ይሰጣል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

መስከረም 3ዐ ቀን 2ዐዐ4 ዓ.ም.

አዲስ አበባ፡፡

 

prev
next

ቦርዱ ከፖለቲካ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት አደረገ

ሚያዝያ 2ቀን 2004 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከፖለቲካ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ጋር  የጋራ ምክክር መድረክ በሂልተን ሆቴል ቅዳሜ መጋቢት 22 ቀን 2004 ዓ.ም ፓርቲዎቹ ማሟላት የሚገባቸውን ድንጋጌዎችና አፈፃፀሞች አስመልክቶ  ውይይት አካሄደ፡፡ የቦርዱ ሰብሰቢ ፕሮፌሰር መርጋ በቃና እንደገለጹት መመዘኛውን ካላሟሉት የፖለቲካ ፓርቲ ከፍተኛ አመራር ጋር የሚደረገው ውይይት ፓርቲዎቹ ማሟላት የሚገባቸውን ድንጋጌዎችና ...

ሙሉ ዜና

ቦርዱ ለሚዲያ ባለሙያዎች በምርጫ ዙሪያ ግንዛቤ ማስጨበጫ ሰጠ

መጋቢት 6 ቀን 2004 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተጣለበትን ህገ-መንግስታዊ ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት ከፌዴራልና ክልል ኮሙዩኒኬሽን ኃላፊዎች እና ከሚዲያ ባለሙያዎች ጋር መጋቢት 3 ቀን 2004 ዓ.ም ለአንድ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ  በአዳማ ከተማ አካሄደ፡፡ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ዓላማ የሁሉም መገናኛ ብዙሃን ተቋማት ባለሙያዎች በዲሞክራሲያዊ ምርጫ እና የሚዲያ ሚና፣ የምርጫ ዘገባና ሞኒተሪንግ ...

ሙሉ ዜና

ቦርዱ በመራጮች እና ሥነ ዜጋ ትምህርት አሰጣጥ ላይ የግምገማ አ

መጋቢት 5 ቀን 2004 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ላለፉት አምስት ወራት ሬዲዮን በመጠቀም ህብረሰቡ በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫና በድህረ ምርጫ ላይ ግንዛቤውን እንዲያዳብር የሚያስችል የመራጮችና ሥነ ዜጋ ትምህርት ስርጭት ላይ ለተሰማሩ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች  ከመጋቢት 1-2 ቀን 2004 ዓ.ም የግምገማ አውደ ጥናት በአዳማ ከተማ አካሄደ፡፡ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር መርጋ ...

ሙሉ ዜና
 

አዳዲስ ዝግጅቶች

ለጊዜው ምንም ዝግጅት አልተገኘም
 


ኮፒራይት © 2010
የኢትዮጵያ ብሔራዌ ምርጫ ቦርድ