ቌንቌ | Language
     
 
መግቢያ መመሪያዎች የመራጮች ምዝገባ አፈፃፀም መመሪያ ቁጥር 2/2ዐዐ1 ዓ.ም. (የተሻሻለው)
     
 
Banner

የመራጮች ምዝገባ አፈፃፀም መመሪያ ቁጥር 2/2ዐዐ1 ዓ.ም. (የተሻሻለው) E-mail

አንቀፅ 1.   አውጪው ባለሥልጣን

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተሻሻለው የኢትዮጵያ የምርጫ ህግ አዋጅ ቁጥር 532/1999 ዓ.ም. በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ይህንን መመሪያ አውጥቷል፡፡

አንቀፅ 2.   አጭር ርዕስ

ይህ መመሪያ «የመራጮች ምዝገባ አፈፃፀም መመሪያ    ቁጥር 2/2ዐዐ1 ዓ.ም.» ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡

አንቀፅ 3.   ትርጓሜ

የቃሉ አገባብ ሌላ ትርጉም የሚያሰጠው ካልሆነ   በስተቀር በዚህ መመሪያ ውስጥ@

1.  «ኢ.ፌ.ዲ.ሪ» ማለት የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ነው፡፡

  1. «ቦርድ» ማለት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነው፡፡
  2. «የፖለቲካ ድርጅት ወይም የፖለቲካ ፓርቲ» ማለት የፖለቲካ ፕሮግራሙን በህጋዊ መንገድ ለማራመድ በህግ ተመዝግቦ የሚንቀሳቀስ ቡድን ነው፡፡
  3. «ጠቅላላ ምርጫ» ማለት አግባብ ባለው ህግ መሠረት የሚካሄድ የሕዝብ ተወካዮችና የክልል ምክር ቤቶች አባላት ምርጫ ነው፡፡

ወደ ኮምፒውተሩ አስቀምጥ


 

 

አዳዲስ ዝግጅቶች

ለጊዜው ምንም ዝግጅት አልተገኘም
 


ኮፒራይት © 2010
የኢትዮጵያ ብሔራዌ ምርጫ ቦርድ