|
ለፖለቲካ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል፡፡ |
|
|
|
|
ታህሳስ 3 ቀን 2004 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለፖለቲካ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ደብረዘይት በሚገኘው የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት ከታህሳስ 2-6 ቀን 2004 ዓ.ም ጀምሮ ለ5 ቀናት በሚቆይ በሁለንተናዊ ለውጥ አመራር (Transformational Leadership) ሥልጠና በመሰጠት ላይ ይገኛል፡፡
የፖለቲካ ፓርቲዎች አቅም ለመገንባት በሀገራችን የተጀመረውን የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ሂደት በይበልጥ ለማጠናከር እና ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ ይህ መድረክ የፖለቲካ ፓርቲዎች ያካበቱትን የተለያዩ ልምድና ሃሣብ የሚለዋወጡበት ነው ሲሉ የቦርዱ ሰብሳቢ ፕ/ር መርጋ በቃና ገልጸዋል፡፡
|
|
ሙሉ ዜና...
|
|
|
ቦርዱ ከሲቪክ ማህበራት ጋር የመራጮችና የሥነ-ዜጋ ትምህርት አስመልክቶ ውይይት አካሄደ |
|
|
|
|
ህዳር 23 ቀን 2004 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለኢትዮጵያ ለሴቶች ፌዴሬሽን፣ለኢትዮጵያ መምህራን ማህበር እና ለአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ህዳር 21 ቀን 2004 ዓ.ም የአሰልጣኞች ሥልጠና በአዳማ ከተማ መስጠቱን አስታወቀ፡፡
ቦርዱ በተሻሻለው የምርጫ ህግ አዋጅ ቁጥር 532/1999 መሰረት መራጩ ህዝብ ስለምርጫ በቂ ግንዘቤ እንዲያገኝ ለማስቻል የመራጮችና የሥነ- ዜጋ ትምህርትን የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም በቅደመ ምርጫ፣ በምርጫ ወቀትና በድህረ ምርጫ መከናወን ስለሚገባቸው ሁኔታዎች ለህብረተሰቡ በማዳረስ ላይ መሆኑ የቦርዱ ሰብሳቢ ፕ/ር መርጋ በቃና አስታውቀዋል ። በዚህ ረገድ ቦርዱ የተለያዩ አበረታች ተግባራትን በማከናወኑ የመራጩ ሕዝብ ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል፡፡
|
|
ሙሉ ዜና...
|
|
ቦርዱ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር የጋር ምክክር አደረገ |
|
|
|
|
ህዳር 21 ቀን 2004 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከፖሊቲካ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በተሻሻለው የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 573/2000 ዓ.ም የጋር ምክክር መድረክ በአዳማ ከተማ አካሄደ። የቦርዱ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር መርጋ በቃና በምክክር መድረኩ ላይ አንደገለፁት ቦርዱ ባለፉት ሁለት አሥርት አመታት የጠቅላላ ፣ የአካባቢ፣ የማሟያ ፣ የድጋሚ ምርጫ እና የህዝብ ውሳኔዎችን ነፃ፣ ፍትሃዊና በገለልተኝነት በማስፈጸም የተጣለበትን ህዝባዊና አገራዊ አደራ በአግባቡ እየተወጣ መሆኑን እና ቦርዱ በህገመንግሥታችን፣ በምርጫ ህግ እና በፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ ህግ በተሰጠው ሥልጣንና ኃላፊነት ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችን እየመዘገበ ፣በህጉ መሠረት እየተከታተለና እያስተናገደ ይገኛል ብለዋል፡፡
|
|
ሙሉ ዜና...
|
|
በምርጫ ክልል ማካለል ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ፡፡ |
|
|
|
|
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በምርጫ ክልል ማካለል ላይ የሰጠውን ስልጠና በአገሪቱ ለሚካሄደው የማካለል ስራ ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው የቦርዱ ሰብሳቢ ገለፁ፡፡ የቦርዱ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር መርጋ በቃና እንደገለፁት ስልጠናው በምርጫ ክልል ማካለል ዙሪያ መልካም ተሞክሮና እና መሰረታዊ ዕውቀት የተገኘበት በመሆኑ የተገኘውን ዕውቀት ወደ ተግባር በማሸጋገር የበኩላችንን መወጣት ይኖርብናል ብለዋል፡፡
ይህ ስልጠና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከ Building Resources in Democracy and Good Governance for Electoral Assistance (BRIDGE) በመተባበር ያዘጋጀው ስልጠና ነው፡፡ በዚህ ስልጠና ላይ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አባላት፣ የጽ/ቤቱ እና የመምሪያ ኃላፊዎች፣ የቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ ከፌዴሬሽን ም/ቤት፣ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን፣ ከእንባ ጠባቂ ተቋም፣ ከፌዴራል ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን፣ የክልሎች እና የከተሞች ርእሰ መስተዳድር ኃላፊዎች፣ ከዘጠኙ የክልል እና ሁለት የከተማ አስተዳድር ምክርቤቶች፣ ከማዕከላዊ ስታስቲክስ ባለስልጣን እና ከኢትዮጵያ ካርታ ስራዎች ኤጀንሲ የተወከሉ አካላት ተካፍለዋል፡፡
|
|
ሙሉ ዜና...
|
|
ቦርዱ ከመገናኛ ብዙሃን ጋር ምክክር አደረገ |
|
|
|
|
ሐምሌ 25 ቀን 2003ዓ.ም
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመራጮችና በሥነ-ዜጋ ትምህርት አሰጣጥ ላይ ያተኮረና የሕዝቡን ግንዛቤ ለማሳደግ የሚያስችል ከክልል መገናኛ ብዙሃን ጋር ከሐምሌ 22-23 ቀን 2003 ዓ.ም ለሁለት ቀናት በአዳማ ከተማ ያካሄደውን የጋራ ምክክር አጠናቀቀ።
የቦርዱ ሰብሳቢ ክቡር ፕ/ር መርጋ በቃና እንደገለጹት የዚህ ምክክር ዋና ዓላማ መራጩ ህዝብ ስለ ምርጫ በቂ ግንዛቤ እንዲያገኝ ለማስቻል፣ የመራጮች እና የሥነ ዜጋ ትምህርት የተለያዩ የማስተማሪያ ዘዴዎችን በመጠቀም በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫ እና በድህረ ምርጫ ወቅቶች ለህብረተሰቡ የማድረስ ኃላፊነት ስላለበት ከመገናኛ ብዙሃን ጋር በትምህርቱ አሰጣጥ ስነ-ዘዴ ላይ ለመምከር ነው ብለዋል።
|
|
ሙሉ ዜና...
|
|
|
|
|
|
|
page 1 of 12 |