|
በ ግንቦት 15 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. በመላው ሀገሪቱ የተካሄደው አራተኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ ውጤት በ2002 ዓ.ም ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በተካሄደው አገር አቀፍ ምርጫ ዕጩዎች ያገኙት ጠቅላላ ድምፅ በ2002 ዓ.ም በተካሄደው አገር አቀፍ የክልል ምክር ቤት አባላት ምርጫ ዕጩዎች ያገኙት ጠቅላላ ድምፅ
በኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ፀድቆ ይፋ የተደረገ ግንቦት 15 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. የተካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ግንቦት 15 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. በመላው ሀገሪቱ አራተኛውን ዙር ጠቅላላ ምርጫ ለማስፈፀም ባወጣው የምርጫ አፈፃፀም የጊዜ ሠሌዳ መሠረት ምርጫው የተረጋጋ፣ ቀልጣፋ፣ ነፃ፣ ፍትሃዊ፣ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊና የሕዝብ አመኔታ በተረጋገጠበት መልኩ ተጠናቋል፡፡ የምርጫው አጠቃላይ ውጤት ሰኔ 14 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. በቦርዱ ፀድቆ ለሕዝብ ይፋ እንደሚደረግ ቀድሞ በወጣው የምርጫ አፈፃፀም የጊዜ ሠሌዳ ተገልጿል፡፡ በተሻሻለው የምርጫ ሕግ አዋጅ ቁጥር 532/1999 ዓ.ም አንቀፅ 76 ንዑስ አንቀፅ 5 መሠረት ቦርዱ በአጠቃላይ የምርጫው ውጤት ከየምርጫ ክልሉ ተጠናቆ እስከሚደርሰው ድረስ ከግንቦት 16 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. ጀምሮ ከየምርጫ ክልሉ የመጣለትን፣
ግንቦት 16፣ 17 እና 19 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. በቦርዱ ጽሕፈት ቤት ለሀገር ውስጥና ለውጪ የመገናኛ ብዙሃን ይፋ አድርጓል፡፡ ቦርዱ ሰኔ 11 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. ባካሄደው 149ኛ አስቸኳይ ስብሰባው፣ - ግንቦት 15 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. በመላው ሀገሪቱ የተካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት ከየምርጫ ክልሉ ተጠቃሎ ለቦርዱ መድረሱን፣ - በአሁኑ ጊዜ ህጉን ተከትሎ ለቦርዱ ቀርቦ ውሣኔ ያላገኘ አቤቱታ አለመኖሩን በማረጋገጥና ውጤቱን በጥልቀት መርምሮ በማፅደቅ ለሕዝብ ይፋ እንዲሆን ወስኗል፡፡ በመሆኑም ግንቦት 15 ቀን በመላው ሀገሪቱ የተካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት ከዚህ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡ 1ኛ/ በምርጫው 63 የፖለቲካ ድርጅቶች ተሳትፈው 1.1 ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ ወንድ 1,916 (87.6%) ሴት 272 (12.4%) በጠቅላላም 2,188 ዕጩዎችን፣ 1.2 ለክልል ምክር ቤት ምርጫ ወንድ 4,ዐ21(84.7%) ሴት 725 ( 15.3%) በጠቅላላው 4,746 ዕጩዎችን 1.3 በግል
2ኛ/ ለመምረጥ የተመዘገበው ሕዝብ ወንድ 16,674,280 (52.2%) ሴት 15,252,24ዐ (47.8%) በድምሩ 31,926,52ዐ ነው፡፡ 3ኛ/ ድምፅ የሰጠው ሕዝብ ወንድ 15,617,453 (52.4%) ሴት 14,214,737 (47.6%) በድምሩ 29,832,19ዐ ነው፡፡
4ኛ/ ከተመዘገበው ውስጥ ድምፅ የሰጠ መራጭ 93.4 በመቶ ነው፡፡ ከተመዘገበው ውስጥ ድምፅ ያልሰጠው መራጭ 6.6 በመቶ ነው፡፡ 1. የጠቅላላ ምርጫ ውጤት 1.1 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ምርጫ ውጤት በጠቅላላው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ ከተካሄደባቸው 547 የምርጫ ክልሎች ውስጥ፣
አሸንፈዋል፡፡ 2. የክልል ምክር ቤት አባላት ምርጫ ውጤት
በመላው ሀገሪቱ በ9 ክልል ምክር ቤቶች ምርጫ ተካሂዷል፡፡ ውጤቱም ከዚህ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡ 2.1 ትግራይ የትግራይ ክልል ምክር ቤት 152 መቀመጫዎች አለው፡፡
2.2. አፋር የአፋር ክልል ምክር ቤት 96 መቀመጫዎች አለው፡፡
2.3. አማራ የአማራ ክልል ምክር ቤት 294 መቀመጫዎች አለው፡፡
2.4. ኦሮሚያ የኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት 537 መቀመጫዎች አለው፡፡
2.5. ሶማሌ የሶማሌ ክልል ምክር ቤት 186 መቀመጫዎች አለው፡፡
2.6 ቤንሻንጉል ጉሙዝ የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት 99 መቀመጫዎች አለው፡፡
2.7. የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች
2.8. የጋምቤላ ሕዝቦች የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት 156 መቀመጫዎች አለው፡፡
2.9. የሐረሪ ሕዝብ የሐረሪ ሕዝብ ክልል ምክር ቤት 36 መቀመጫዎች አለው፡፡
3. ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለክልል ምክር ቤቶች የአሸናፊ የፖለቲካ ድርጅቶችና ዕጩዎች ዝርዝርና ያገኙት ድምፅ በቦርዱ ጽሕፈት ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ቦርዱ ጥቅምት 24 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. ባወጣው የምርጫ አፈፃፀም የጊዜ ሠሌዳ መሠረት ዛሬ ሰኔ 14 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. ለሕዝብ እነሆ ይፋ ተደርጓል፡፡ ይኸው ዝርዝር በተከታታይ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ይወጣል፡፡ በተጨማሪም በቦርዱ ድህረ ገፅ ዛሬ ተጭኗል፡፡ 4. በተመሳሳይ ሁኔታ ለጠቅላላ ምርጫ በእያንዳንዱ የምርጫ ክልል የተወዳደሩ የፖለቲካ ድርጅቶች ዕጩዎች ያገኙት ድምፅ ዝርዝር ይፋ ተደርጓል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. አዲስ አበባ
II. ግንቦት 22 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. በሶማሌ ክልል የተካሄደው የአካባቢ ምርጫ ውጤት ቦርዱ በልዩ ሁኔታ የካቲት 24 ቀን በ2ዐዐ2 ዓ.ም. ባወጣው የምርጫ አፈፃፀም የጊዜ ሠሌዳ መሠረት በሶማሌ ክልል ግንቦት 22 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. የአካባቢ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሀዊ፣ ሠላማዊ ዴሞክራሲያዊና የሕዝብ አመኔታን ባተረፈ መልኩ መከናወኑን አረጋግጧል፡፡ በዚሁ መሠረት ቦርዱ በክልሉ የተካሄደውን የአካባቢ ምርጫ ውጤት መርምሮ እና አፅድቆ ሰኔ 14 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. ይፋ እንዲሆን በወሰነው መሠረት ከዚህ እንደሚከተለው እንገልፃለን፡፡ 1. የጅጅጋ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት አባላት ምርጫ ውጤት
2. የወረዳ ምክር ቤት አባላት ምርጫ ውጤት
3. የቀበሌ ምክር ቤት አባላት ምርጫ ውጤት
የሶማሌ ክልል የአካባቢ ምርጫ ውጤት ዝርዝርም በቦርዱ ጽሕፈት ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ዛሬ ሰኔ 14 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. ይፋ ተደርጓል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. አዲስ አበባ
በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፀደቀ ግንቦት 15 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. በመላው ሀገሪቱ የተካሄደው አራተኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ የክልል ምክር ቤቶች አጠቃላይ ውጤት
ዘጠኝ ክልሎች በድምሩ 1,9ዐ4 የክልል ምክር ቤቶች መቀመጫዎች አላቸው፡፡
በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፀደቀ ግንቦት 15 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም. በመላው ሀገሪቱ የተካሄደው አራተኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አጠቃላይ ውጤት
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 547 መቀመጫዎች አሉት፡፡
|